የቦንጋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዕጩ መምህራንን በዛሬው ዕለት አስመረቀ፡፡

የቦንጋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዕጩ መምህራንን በዛሬው ዕለት አስመረቀ፡፡
ቦንጋ፣ ሰኔ ፣ 25፣ 2014(ቦመትኮ) የቦንጋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ 856 ዕጩ መምህራንን በዛሬው ዕለት አስመረቀ
የቦንጋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት በመደበኛ መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን 856 ዕጩ መምህራንን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ኮሌጁ በዛሬው ዕለት በ 20 በተለያዩ የትምህርት መስኮች 473 ወንዶችና 383 ሴት በድምሩ 856 ዕጩ መምህራንን አስመርቋል፡፡
የኮሌጁ ዲን አቶ አንተነህ አየለ ለተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን ባስስተላለፉበት ወቅት እንደተናገሩት ኮሌጁ በሰርተፊከት ደረጃ ለማሰልጠን ከተመሰረተበት ጊዜያት አንስቶ በመደበኛና በተከታታይ የስልጠና መረሃ ግብሮች በሰርቲፊኬትና በዲፕሎማ ደረጃ ከ38 ሺ 6መቶ 31በላይ መምህራንን በማሰልጠን ወደ መምህርነት ሙያ ማሰማራቱን ገልፀዋል።